Build Your Dream

ጥምቀትን የወልድያ ከተማ መገለጫ ለማድረግ እየተሠራ ነው

ወልድያ: ጥር 09/2017 ዓ.ም የከተማ አሥተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዱባለ አብራሬ የጥምቀት በዓል በወልድያ ከተማ ከ1770ዎቹ ጀምሮ በሃይማኖታዊ እና በባሕላዊ ክዋኔ እየተከበረ መቆየቱን ገልጸዋል።

ይህን የከተማዋን መገለጫ በዓል በማጉላት እስከ 2025 ዓ.ም ድረስ የጎብኝዎች መዳረሻ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ ነውም ብለዋል።

ለዚህም የሃይማኖት አባቶች ሃይማኖታዊ መልኩን፣ መንግሥት ደግሞ ማኅበረሰባዊ ኹነቱን አጉልቶ በመገንባት ሚናቸውን ለመወጣት መግባባት ላይ ተደርሷል ነው ያሉት።

የዚህ ዕቅድ ጅማሮ የኾነው የ2017 የጥምቀት በዓል በድምቀት እንዲከበር ከሃይማኖት አባቶች፣ ከወጣቶች ከጸጥታ አካላት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር ብሎም ቀድመ ዝግጅት በማድረግ በዓሉን በሰላም ለማክበር ተሠርቷል ብለዋል።

ወልድያን እንደቀድሞ ስሟ ገነት ለማድረግ ከተያዙት ኘሮጀክቶች አንዱ የኾነውን የጥምቀት በዓል ድምቀት በማሳመር ማኅበረሰቡ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ነው ከንቲባው ያሳሰቡት።

ከአለባበስ እና ጭፈራ ጀምሮ ቀድሞ የነበረውን የከተማዋን ገጽታ የሚገነባ ክዋኔ እንዲኖር ወጣቱ ኀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።

ከጸጥታ አኳያም የመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የኅብረተሰቡን ደኅንነት ለመጠበቅ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረው ኅብረተሰቡም ራሱን እና ሃይማኖታዊ እሴቱን እንዲጠብቅ ጠይቀዋል።

Share:

More Posts

የቱሪዝም ምንነትና መስህብ ሀብቶቻችን

የአለም ህዝቦችን በማቀራረብ የባህል ልውውጥ እንዲኖር በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና የሚጫወት ትልቅ የኢንዱስትሪ መስክ እየሆነ መምጣቱ ሁሉም እየመሰከረለት የመጣ መስክ ነው፡፡ ሰዎች ለተለያዩ አላማዎች ከቦታ

የቅርስ ምንነት እና ትርጉም

ይዘት መግቢያ ሐገራችን ኢትዮጲያ ካላት የተፈጥሮ ሐብት ቀደምት ህዝቦች የስራ ውጤት የሆኑት ቅርሶች ባለቤት መሆኗ የሚታዎቅ ነው፡፡ ለምሳሌ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትም የበርካታ ሰው ሰራሽና

ባህል የማንነታችን  መገለጫ ነዉ!

ባህል፡- እንደ ማህበረሰብ ሳይንስ አጥኝዎች ትርጉም የሰዉ ልጅ ባህርይ ፣ እምነት ፣ ዝንባሌ ፣ እሴት እና አስተሳሰብ እንዲሁም በማህበራዊ ኑሯቸዉ ዉስጥ የሚማሩት ፣ የሚፈጥሩት እና

 ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች

የሰው ልጅ በህይት ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቱ መርካት አለበት፡፡ ከዚህ ዉጭ የሚፈፅማቸው ግን ደባል ወይም ትርፍ ነገሮች ናቸው፡፡ እነዚህም ትርፍ ነገሮች ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች ወይም

Send Us A Message

Scroll to Top